በእግር ኳስ ተጫዋቹ አለልኝ አዘነ ግድያ ላይ በሁለት ፈረቃዎች የፍርድ ውሳኔ ለመስጠት የተሰየመው የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ።
1ኛ ተከሳሽ የአለልኝ ባለቤት እና 2ኛ ተከሳሽ የባለቤቱ እህት ባል መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ/ም ከሌሊቱ 5፡30 እስከ 8 ሰዓት ገደማ ባለዉ ጊዜ በአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ነጭ ሳር ቀበሌ ልማት ሰፈር ‘ ሃይላንድ ‘ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በተቀነባበረ ሁኔታ የ26 አመቱን ወጣት በመግደል ።
እራሱን ያጠፋ እንዲመስል በማድረግ የግዲያ ወንጀል መፈፀማቸው በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች በመረጋገጡ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ ብሏቸዋል ።
ከሰዓት በኃላ የፍርድ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ይዞ የነበረዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት መደበኛ ችሎት የዐቃቤ ሕግና የተከሳሾችን ጠበቃ የቅጣት አስተያየት ካደመጠ በኋላ ዉሳኔዉን ወደ ሀምሌ 15/2017 ዓ/ም አሸጋግሯል።
