በጋምቤላ ክልል   ከ 42 ሺህ በላይ ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ተነገረ

Date:

በክልሉ ሰብአዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸዉ  ከ 42 ሺ በላይ ዜጎች በጎርፍ እና በግጭት ምክንያት ተፈናቅለዋል።

በጋምቤላ ክልል ያሉ የሰብአዊ  ተራድኦ ድርጅቶችም የተደራሽነት ችግር አጋጥሟቸዋል ተብሏል።

የተራድኦ ድርጅቶቹ የሰብአዊ ድጋፍን በተቀናጀ መልኩ ለማሰራጨት ማስተባበር ላይ ክፍተት እንዳጋጠማቸው ሰምተናል።

የጋምቤላ ክልል የአደጋ ስጋት  ስራ አመራር አገልግሎት ዳይሬክተር ጃክ ጆይ እንደገለፁት ድርጅቶቹ በሚጠበቀዉ መጠን እየሰሩ አለመሆኑን ገልፀዋል።

በተለይም እነዚህን የሰብአዊ ተራድኦ ድርጅቶች የሚያስተባብራቸዉ ተቋም የ ተመድ የሰብአዊ ማስተባበሪያ ኦቻ ሲሆን ቢሮዉ  ጋምቤላ ከተማ ላይ አለመሆኑ አንዱ ምክንያት እንደሆነ አንስተዋል።

ቢሮዉ መገኛዉ አሶሳ ላይ በመሆኑ ተቋማቱን ለሰብአዊ ድጋፍ ለማስተባበር ባለመቻል  ክፍተት እየፈጠረ ስለመሆኑ የጋምቤላ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር አገልግሎት ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።

ዳይሬክተሩ በክልሉ  42 ሺህ 374 ሰብአዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸዉ  የጎርፍ እና የግጭት ተፈናቃዩች በክልሉ አሉ ብለዋል።

በክልሉ  ካቢኔ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር  ስትራቴጂክ ኘላን ቢፀድቅም ለተግባራዊነቱ በጀት የማፈላለግ ስራዉን የአለምአቀፍ ተቋማት ያደረጉት  የ ፈንድ  ገደብ እክል ፈጥሯል ሲሉ ገልፀዋል።

ኢትዩ ኤፍም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...