አምስት ህፃናት በከሰል ጭስ ታፍነው ህይወታቸው አለፈ

Date:

በትግራይ ዓድዋ ከተማ አሉላ ጣቢያ (እንዳ ገብርኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ)፣ በታላቁ የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል ላይ፣ ባጋጠመ አሳዛኝ አደጋ የ5 ህፃናት ሕይወት ማለፉ ተገለጸ፡፡

ሕፃናቱ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ተኝተው ሳለ በከሰል ጭስ (Carbon Monoxide) መታፈን በድንገት ሕይወታቸው ማለፉን የዓድዋ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል፡፡

ከእነዚህም መካከል ሦስቱ የአንድ ቤት ልጆች ሲሆኑ፣ ሁለቱ ደግሞ የአባወራው እህት ልጆች ናቸው ተብሏል።

አሰተዳደሩ ባስተላለፈው የሃዘን መግለጫ፤ “የዓድዋ ከተማ አስተዳደርና መላው የከተማዋ ነዋሪዎች በዚህ ድንገተኛና ልብ የሚሰብር መርዶ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጹ፤ ለወላጆች፣ ለቤተሰቦችና ለወዳጅ ዘመዶች መጽናናትንና ብርታትን ይመኛሉ። ” ብሏል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...