በትግራይ ዓድዋ ከተማ አሉላ ጣቢያ (እንዳ ገብርኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ)፣ በታላቁ የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል ላይ፣ ባጋጠመ አሳዛኝ አደጋ የ5 ህፃናት ሕይወት ማለፉ ተገለጸ፡፡
ሕፃናቱ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ተኝተው ሳለ በከሰል ጭስ (Carbon Monoxide) መታፈን በድንገት ሕይወታቸው ማለፉን የዓድዋ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል፡፡
ከእነዚህም መካከል ሦስቱ የአንድ ቤት ልጆች ሲሆኑ፣ ሁለቱ ደግሞ የአባወራው እህት ልጆች ናቸው ተብሏል።
አሰተዳደሩ ባስተላለፈው የሃዘን መግለጫ፤ “የዓድዋ ከተማ አስተዳደርና መላው የከተማዋ ነዋሪዎች በዚህ ድንገተኛና ልብ የሚሰብር መርዶ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጹ፤ ለወላጆች፣ ለቤተሰቦችና ለወዳጅ ዘመዶች መጽናናትንና ብርታትን ይመኛሉ። ” ብሏል፡፡
