ዛሬ ምሽት በእንግሊዝ ካራባኦ ካፕ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ አርሰናል እና ቼልሲ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
በሚኬል አርቴታ የሚመራው አርሰናል በስታምፎርድ ብሪጅ በተደረገው የመጀመሪያ ዙር የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ 3 ለ 2 ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በዚህ የውድድር ዓመት አራት ዋንጫ ለማሳካት እየተፋለመ ይገኛል፡፡
የሁለቱ ቡድኖች ተጠባቂ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ ምሽት 5 ሰዓት ላይ በኢምሬትስ ስታዲየም መደረግ ይጀምራል፡፡
የአርሰናል እና ቼልሲ የድምር ውጤት አሸናፊ በፍጻሜው ከማንቼስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ አሸናፊ ጋር ለዋንጫው የሚፋለም ይሆናል፡፡
