አርሰናል 4ለዜሮ ሲያሸንፍ ማንቼስተር ዩናይትድ ተሸነፈ

Date:

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከሜዳው ውጪ ኢፕስዊች ታውንን ሲያሸንፍ ማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ አርሰናል ኢፕስዊች ታውንን 4 ለ 0 አሸንፏል፡፡

አርሰናል የጨዋታ ብልጫ በወሰደበት ጨዋታ ሊያንድሮ ትሮሳርድ (2)፣ ጋብርኤል ማርቲኔሊ እና ኢታን ኒዋኔሪ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

በተመሳሳይ በተደረገ ሌላ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ፓብሎ ሳራቢያ ባስቆጠራት ግብ በወልቭስ 1 ለ 0 ተሸንፏል፡፡

ሽንፈቱ ማንቼስተር በውድድር ዘመኑ ያስተናገደው 15ኛ ጨዋታ ሆኖ ተመዝግቧል።

በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገው የቼልሲ እና ፉልሃም ጨዋታ ድራማዊ ትዕይንትን አስተናግዶ በቼልሲ 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡

በጨዋታው ፉልሃም በአሌክስ ኢዮቢ ግብ እስከ 84ኛው ደቂቃ ሲመራ ቢቆይም ታዳጊው ትሬቅ ጆርጅ በ85 እንዲሁም ፔድሮ ኔቶ በጭማሪ ደቂቃ ግብ አስቆጥረው ቼልሲ አሸናፊ ሆኗል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...