በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከሜዳው ውጪ ኢፕስዊች ታውንን ሲያሸንፍ ማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ አርሰናል ኢፕስዊች ታውንን 4 ለ 0 አሸንፏል፡፡
አርሰናል የጨዋታ ብልጫ በወሰደበት ጨዋታ ሊያንድሮ ትሮሳርድ (2)፣ ጋብርኤል ማርቲኔሊ እና ኢታን ኒዋኔሪ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
በተመሳሳይ በተደረገ ሌላ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ፓብሎ ሳራቢያ ባስቆጠራት ግብ በወልቭስ 1 ለ 0 ተሸንፏል፡፡
ሽንፈቱ ማንቼስተር በውድድር ዘመኑ ያስተናገደው 15ኛ ጨዋታ ሆኖ ተመዝግቧል።
በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገው የቼልሲ እና ፉልሃም ጨዋታ ድራማዊ ትዕይንትን አስተናግዶ በቼልሲ 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
በጨዋታው ፉልሃም በአሌክስ ኢዮቢ ግብ እስከ 84ኛው ደቂቃ ሲመራ ቢቆይም ታዳጊው ትሬቅ ጆርጅ በ85 እንዲሁም ፔድሮ ኔቶ በጭማሪ ደቂቃ ግብ አስቆጥረው ቼልሲ አሸናፊ ሆኗል፡፡
