አስካሪ ሜታልስ በኢትዮጵያ ግዙፍ የወርቅ ፕሮጀክት ገዛ

Date:

አውስትራሊያዊው የአክሲዮን ኩባንያ አስካሪ ሜታልስ በኢትዮጵያ የሚገኘውን ትልቅ የኒጆ ወርቅ ፕሮጀክት ለመግዛት ስምምነት ላይ መድረሱን አስታወቀ። ግዢው ኩባንያው በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንዱስትሪ ውስጥ ትልቅ ድርሻ እንዲይዝ የሚያስችለው ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ 1,174 ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት አለው።

ይህ የተፈፀመው ደግሞ የፕሮጀክቱ ባለቤት ከነበረው ዢንግሹ ማይኒንግ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት የተባለውን ኩባንያ ላይ 100% ድርሻ በመግዛት ነው።

ይህ ግዢ አስካሪ ሜታልስ ባለፉት 4 ዓመታት በኢትዮጵያውያን አጋሮች ሲስተዳደር የነበረውን የኒጆ ፕሮጀክት ላይ ሙሉ ህጋዊ እና የባለቤትነት መብትን የሚያስገኝለት ይሆናል ተብሏል።

የኒጆ ፕሮጀክት በአረቢያ-ኑቢያን ጋሻ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህ የበለፀገ የጂኦሎጂካል ክልል በግብፅ፣ ሱዳን፣ ኤርትራ፣ ኢትዮጵያ፣ ሳውዲ አረቢያ እና የመን በሚገኙ በርካታ ሚሊዮን አውንስ የወርቅ ክምችቶች ይታወቃል።

የኒጆ የወርቅ ፕሮጀክት እንደ ካናዳዊው ማዕድን አውጪ አላይድ ጎልድ ባለቤትነት ስር ያለው የ3.4 ሚሊዮን አውንስ የኩርሙክ ማዕድን ማውጫ እና የኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር ባለቤትነት ስር ያለውን የ1.7 ሚሊዮን አውንስ ቱሉ ካፒ ማዕድን ማውጫ በሚያዋስነው ተመሳሳይ የግሪን ስቶን ቤልት ላይ ይገኛል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...