አዋሽ ባንክ 25 ሚሊዮን ብር በድጋፍ ሰጠ

Date:

አዋሽ ባንክ የ1447ኛውን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ በሸራተን አዲስ ሆቴል ባዘጋጀው የኢፍጣር መርሃ-ግብር ላይ ለሰባት ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የ25 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አበረከተ።

ድጋፉ የተደረገላቸው ወንድም ካሊድ ፋውንዴሽን፣ ዘ ችልድረንስ ኸርት ፈንድ እና እዝነትን ጨምሮ በሕፃናት፣ አረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ላይ ለሚሠሩ ተቋማት ነው። ባንኩ ከዚህ በተጨማሪ በ52 የሀገሪቱ ከተሞች ለሚገኙ 2,600 አባወራዎች የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል።

የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው እንደተናገሩት፤ አዋሽ ባንክ ላለፉት 31 ዓመታት በማዕድ ማጋራት፣ በጤና እና በቤት ግንባታ ዘርፎች ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ ቆይቷል።

በአሁኑ ወቅት ባንኩ ከ1,005 በላይ ቅርንጫፎች ያሉት ሲሆን፣ ከ3.5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የሪባ-ነፃ የባንክ አገልግሎት ደንበኞች ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ የሃላል ፋይናንስ ማቅረብ ችሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...