አያቶላ ኻሜኒ ሕዝባቸው “በጥንካሬው ጸንቶ እንዲቀጥል” ጥሪ አቀረቡ

Date:

የምስሉ መግለጫ,አያቶላህ አሊ ኻሜኒ
የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ለኢራን ሕዝብ “ጠላት እንደምትፈሩት ከተሰማው አይለቃችሁም” ሲሉ ሕዝባቸው በጥንካሬው እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

መሪው በኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ሕዝባቸውን “እስከ ዛሬ ድረስ በነበራችሁ ባህርይ ቀጥሉ፣ ይህንንም ባህርያችሁን በጥንካሬ በመያዝ ጸንታችሁ ቀጥሉ” ብለዋል።

ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ እስራኤል ኢራን ውስጥ የፈጸመችው ጥቃት ተከትሎ ሁለቱ አገራት አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ አውዳሚ ጥቃት መፈጸማቸውን ቀጥለዋል።

በእስካሁኑ ጥቃት የኒውክሌር ማዕከላት፣ ወታደራዊ እና የመንግሥት ተቋማት፣ የመገናኛ ብዙኃን፣ የሰላማዊ ሰዎች መኖሪያ እና ተቋማት ጉዳት ደርሶባቸዋል። በሁለቱም ወገን በመቶቹ የሚቆጠሩ ሰዎች መገደላቸውን እና ሺዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው እየተነገረ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...