ኢሰመኮ በአማራ ክልል በአምስት ማረሚያ ቤቶች ላይ ክትትል ማድረጉን ገለፀ

Date:

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮምሽን ባህርዳር ቅርንጫፍ በበጀት አመቱ 9 ወራት 163 አቤቱታዎች ተቀብያለሁ ብሏል።

የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ አለባቸው ብርሃኑ ከደረሱ አቤቱታዎች 15 ያህሉ ብቻ መፍትሄ እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል።

ፅህፈት ቤቱ በማረሚያ ቤቶች፣ በፖሊስ ጣቢያዎችና ክትትል በሚያስፈልጋቸው ሌሎች ቦታዎች ላይ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ሀላፊዉ ገልፀዋል።

ሆኖም በርካታ ማረሚያ ቤቶች በክልሉ ቢኖሩም በበጀት ዓመቱ ክትትል የተደረገባቸዉ አምስት ማረሚያ ቤቶች ናቸዉ ተብሏል።

የሕዝብ ተወካዮች ም/ ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በበኩሉ በማረሚያ ቤቶች እያደረገ የሚገኘው የክትትልና ምርመራ ስራ ከክልሉ ነባራዊ የፀጥታ ሁኔታ አንጻር ሲታይ መልካም የሚባል ነዉ ሲል ገልፆል።

በክልሉ ከሰብዓዊ መብቶች አኳያ የሚፈጠሩ ጥሰቶች በየትኛው፤ አካል ይፈፀሙ ምርመራ እንደሚደረግ ፅህፈት ቤቱ አንስቷል።

የኢሰመኮ ባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ተደራሽነቱን በማስፋት የክትትል እና ምርመራ ስራውን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገልፆል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...