ከትናንት በስትያ በተጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌትክስ ሻምፒዮና በ1500ሜ ክለቧን መቻልን በመወከል 2ኛ በመውጣት ውድድራን ያጠናቀቀችው የመቻል ስፖርት ከለብ አትሌት ትዕግስት ግርማ
ለቶኪዮ የዓለም አትሌትክስ ሻፒዮና ሚኒማ ለማምጣት ወደ ኳታር ዶሃ ዳይመንድ ሊግ በማቅናት ላይ እያለች ነው በቦሌ አለማቀፍ አየር ማረፊያ ከክለቧ በተላለፈ ደብደቤ መሰረት የታሰረችው።
የመረጃ ምንጮቻችን እንደገለፁት የተያዘችበት ምክንያት አትሌቷ ከዚህ በፊት ክለቧን ሳታስፈቅድ ወደ አውሮፓ ለውድድር በመሄዷ ምክንያት እንደሆነ የገለፁ ሲሆን ለምን ሳታስፈቅድ ሄደች የሚል ጥያቄ ጠይቄአቸው ነበረ ፤ለተጠየቁት ጥያቄ ሲመልሱም አትሌቷ አሰልጣኟን ጠይቃ በቃል እንደፈቀደላት ከውድድር ከተመለሰችም በኋላ ጉዳዩ እንደታየና እንደተፈታላት የገለፁ ሲሆን ከመፈታቱ በፊት በተላለፈ ደብዳቤ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ለኢትዮራነርስ ገልፀዋል።
ጉዳዩ የሚመለከታችሁ በሙሉ ከክለቧ ጋር በመነጋገርና ችግረሩን በመፍታት ለአትሌቷ መፍትሔ እንዲመጣና ወደ ውድድሯ እንድታቀና አስፈላጊውን ሁሉ ትብብር እንዲደረግላት በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን ብለዋል የአትሌቷ የቅርብ የሆኑ የመረጃ ምንጮቻችን ።
Via Ethio Runners
