ኢባትሎ የሀገሪቱን የትራንስፖርት አቅም የሚያሳድጉ 100 አዳዲስ ተሽከርካሪዎችን ስራ አስጀመረ

Date:

​የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ (ኢባትሎ) የሀገሪቱን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አቅም ይበልጥ ለማሳደግና ቀልጣፋ አገልግሎትን ለማረጋገጥ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ያረፈባቸውን 100 አዳዲስ ተሽከርካሪዎች በዛሬው ዕለት በይፋ ስራ አስጀምሯል።

የኢባትሎ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ በወቅቱ እንደተናገሩት፣ እነዚህ ተሽከርካሪዎች ድርጅቱ ካሉት 556 ተሽከርካሪዎች ጋር ተዳምረው የጭነት ፍሰቱን ለማሳለጥና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለመደገፍ ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለፁት፤ አሽከርካሪዎቹ የኢትዮጵያን ስም በድንበር ተሻጋሪ መንገዶች ላይ ከፍ ያደረጉ የኢኮኖሚ ጀግኖች መሆናቸውን በመጥቀስ፣ በሀገር ፍቅርና በሙያ ስነ-ምግባር ተግተው ስራቸውን እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

በመርሃ-ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ተሽከርካሪዎቹን ለአገልግሎት ብቁ በማድረግ ረገድ በቴክኒክና በጥገና ስራ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ የድርጅቱ ሰራተኞች የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...