ኢትዮ ቴሌኮም የ23% አማካይ የዋጋ ማስተካከያ አደረገ

Date:

ኢትዮ ቴሌኮም ለሚድያ አካላት በላከው እና ለደንበኞቹ በተለያዩ ማህበራዊ ገፆቹ ባሰራጨው መግለጫ በአሁኑ ወቅት ያለውን ማክሮ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ፣ የአገልግሎት ጥራትን በዘላቂነት ለማስጠበቅ የታሪፍ ማሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብሏል።

እናም የአገልግሎት ጥራትን በዘላቂነት ለማስጠበቅና የቴክኖሎጂ አቅሙን ለማሳደግ የሚያስችል ስትራቴጂካዊ የታሪፍ ማስተካከያ ይፋ አድርጓል።

በዚህም መሰረት ኢትዮ ቴሌኮም በአማካይ የ23% የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን አስታውቋል።

ይህ ማስተካከያ የደንበኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲቻል ሶስት አበይት ነጥቦችን ማካተቱንም የጠቆመ ሲሆን፡፡ እነዚህም፦

  • የቴሌብር ልዩ ስጦታ ማዕቀፍ፦ በቴሌብር በኩል ጥቅል ሲገዛ የነበረው የ10% ቅናሽ ወደ 20% ከፍ እንዲል ተደርጓል።
  • ዋጋቸው ያልተቀየሩ ጥቅሎች፦ በርካታ ደንበኞች የሚጠቀሙባቸው 38 የተለያዩ ጥቅሎች ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አልተደረገም።
  • ዲጂታል አካታችነትን ለማስቀጠል፦ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚጠቀሙባቸው የ1 ብር፣ የ2 ብር፣ የ5 ብር እና የ1 ሰዓት ጥቅሎች ባሉበት እንዲቀጥሉ ተወስኗል።

ኢትዮ ቴሌኮም የዋጋ  ጭማሪው ለኢትዮጵያውያን የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚነት ቀጣይነት እንዲሁም የሀገሪቱን አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያፋጥን እንዲሆን በማሰብ ተመጣጣኝ  እንዲሆን ማድረጉን ገልፃል፡፡

EthioTelecom

etbusinessview

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...