“ኦሮሚያ ክልል “ጠፍቶ” ለማየት የሚመኙ አካላት አሉ”

Date:

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ባለውና ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ የመንግሥት አመራሮች በሚሳተፉበት መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ኦሮሚያ ክልል “ጠፍቶ” ለማየት የሚመኙና ኦሮሚያ የሚለውን ቃል መስማት የማይፈልጉ አካላት አሉ ሲሉ ገልጸዋል።

ይህ ምኞት “በፍጹም” ሊሳካ እንደማይችል የገለጹት ርዕሰ መሥተዳድሩ፣ ይልቁንም ክልሉ ወደፊት ይበልጥ እየጠነከረ፣ መሬት እየያዘና ውጤታማ እየሆነ እንደሚሄድ በኦሮምኛ ቋንቋ ባደረጉት ንግግር አመልክተዋል፡፡

ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ኦሮሚያ ክልል ጠፍቶ ማየት ይፈልጋሉ ያሏቸውን አካላት ማንነት ግን በስም ለይተው በንግግራቸው ውስጥ አልጠቀሱም።

አቶ ሽመልስ ይህን የተናገሩት፣ የክልሎች አወቃቀር ጉዳይ ለአገራዊ ምክክር ጉባኤው በአጀንዳነት በቀረበበት ማግስት ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ...

ሱልጣን ቢን ኻሊፋ ግሩፕ በኢትዮጵያ በሆቴል ዘርፍ ሊሰማራ ነው

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር...

የአሜሪካ የታክስ ህግ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ሽልማት ስጋት ላይ ጣለ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከዓለም ዋንጫ ሊያገኘው ከሚችለው 50 ሚሊዮን...

ህወሓት ከሌሎች ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር የሚደረግ ጥምረት አስፈላጊ መሆኑን ገለጸ

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ...