ከታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ጋር የተገናኙ ወንጀሎች

Date:

የታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008

  1. ማንኛውም ሰው

ሀ. ከአንድ በላይ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር የወሰደ ወይም ለመውሰድ የሞከረ እንደሆነ፤

ለ. የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥሩን ሌላ ሰው እንዲጠቀምበት የሰጠ፣ ወይም

ሐ. የሌላን ሰው የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር የተጠቀመ እንደሆነ፣ብር 20ሺ የገንዘብ
ቅጣት እና ከአንድ ዓመት እስከ ሦስት ዓመት በሚደርስ ቀላል እስራት ይቀጣል፡፡

  1. ከአንድ በላይ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር የወሰደ ወይም ለመውሰድ የሞከረ እንደሆነ ታክስ ከፋዩ ለወሰደው ወይም ለመውሰድ ለሞከረው ለእያንዳንዱ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር በተናጠል ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
  2. የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ጥቅም ላይ የዋለው በዚህ አዋጅ አንቀጽ 14/6 የታክስ መለያ ቁጥር ባለቤት ለታክስ ወኪሉ መጠቀም እንዲችል በፅሁፍ ሲፈቀድለት እና የታክስ ወኪሉ የታክስ መለያ ቁጥሩን ለባለቤቱ ታክስ ጉዳዮች ብቻ ሲጠቀምበት የዚህ አንቀፅ ንኡስ አንቀፅ 1/ለ/ እና /ሐ/ ተፈፃሚ አይሆኑም፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...