ከ27 ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ በቁጥጥር ስር ዋለ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ በቃሊቲ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ቱሉ ዲምቱ መቆጣጠሪያ ጣቢያ በተደረገ ፍተሻ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 27 ነጥብ 75  ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

በቁጥጥር ስር የዋለው ጥፍጥፍ  ወርቅ ከአንድ ወር በላይ ክትትል ሲደረግበት መቆየቱን የጉምሩክ ኮሚሽን የሕግ ተገዥነት ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ ተናግረዋል፡፡

ጥፍጥፍ ወርቁን በህገወጥ መንገድ በተሽከርከሪ አካል ውስጥ ደብቀው ሲያዘዋውሩ የነበሩ ሶስት ተጠርጣሪዎችና ሁለት ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጸዋል፡፡

የኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ከፋና ዲጂታል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...