ከአውሮፓዊያኑ 2025-2030 ተግባራዊ የሚደረገው ስትራቴጂ፤ በኤ.አይ አስተዳደር፣ በፈጠራና ክህሎት ዘርፎች ኬንያን ግንባር ቀደም ለማድረግ ያለመ ነው።
በተጨማሪም ሀገሪቷ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሥነ-ምህዳር ውስጥ በአፍሪካ ብሎም በዓለማቀፍ ደረጃ ወሳኝ ሚና እንድትጫወት ስትራቴጂው አጋዥ ነዉ ተብሏል።
ስትራቴጂው በሀገሪቱ ብሔራዊ የኤ.አይ የስራ ቡድንና አስተባባሪ ኮሚቴ ከመንግሥት ተቋማት፣ ከግሉ ዘርፍ፣ ከአካዳሚክ፣ ከሲቪል ማህበረሰብና ከዓለማቀፍ አጋሮች ጋር ሰፊ ምክክር በማድረግ መዘጋጀቱ ተጠቁሟል፡፡
ይህ ስትራቴጂ ከአፍሪካ ህብረት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ ጋር የሚጣጣም መሆኑንም ቴክ አፍሪካ ኒውስ አስነብቧል።
