በህገ ወጥ መልኩ በአሜሪካ የሚኖር ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ የምትነግሩበት ጊዜ አሁን ነው

Date:

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በአምባሳደሩ ኤርቪን ማሲንጋ አማካኝነት መልዕክት አስተላልፏል።

በህገወጥ መንገድ ወደ አሜሪካ መግባት፣ ቪዛ ለማግኘት መዋሸት፣ ያለ ህጋዊ የስራ ፍቃድ ስራ መስራትና የቪዛ ጊዜ ካበቃ በኋላ በአሜሪካ መቆየት ከባድ ቅጣት ያስከትላል።

ቅጣቶቹ እስርን፣ ወደ ሃገር መመለስን እና ዳግም ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ መከልከልን እንደሚያካትት ነው አምባሳደሩ የተናገሩት።

አክለውም፥ “በህገ ወጥ መልኩ በአሜሪካ የሚኖር ቤተሰብ ወይም ጓደኛ ካላችሁ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ የምትነግሩበት ጊዜ አሁን ነው” ሲሉ ገልጸዋል።

መልዕክቱ፥ የአሜሪካ መንግስት ሌሎች በህገወጥ መንገድ እንዲገቡ የሚተባበሩት ላይም ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቋል።

አሜሪካ በቅርቡም ህገወጥ ስደትን መከላከል አልቻሉም ባለቻቸው የሃገራት ባለስልጣናት ላይ የቪዛ ገደብ መጣሏን አስታውሰዋል።

በህገወጥ መንገድ መግባት ከሚያስገኘው ጥቅም በላይ ጉዳቱ ያመዝናል ያለው ኤምባሲው ዜጎች የወደፊት ህይወታችን ከመጉዳት እንዲታጠቀቡ እና በህገወጥ መንገድ በአሜሪካ ያሉ ቤተሰቦቻቸውንም በጊዜ እንዲመለሱ ጥሪ እንዲያደርጉ አምባሳደሩ አሳስበዋል።

@Tikvahethmagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...