ዋና ጸሐፊ ከኡጋንዳ የንግድ፣ ኢንዱስትሪ እና ኅብረት ስራ ሚኒስትር ምዌብሳ ፍራንሲስ ጋር ተወያዩ

Date:


ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ሲሆኑ የሁለቱ አካላት ውይይትም በተለይም በኢኮኖሚ እና ቢዝነስ መስች ያሉ እድሎችን ለጋራ ተጠቃሚነት ማዋል እንዲቻል ያግዛል ተብሏል፡፡


በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ለውጦች እና ምቹ የቢዝነስ ከባቢ ለመፍጠር ምክር ቤቱ በሚያከናውናቸው የንግድና ኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን፣ የአቅም ግንባታ፣ የምርምርና አድቮኬሲና ሌሎች ስራዎች ዙሪያ ገልጸውላቸዋል፡፡


ዶክተር ቀነኒሳ ለሚ እንደ ኡጋንዳ ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ጋር በመተባበር በአህጉሩ ያለውን የገበያ እድል መጠቀም እንደሚገባ አብራርተውላቸዋል፡፡


ሚኒስትሩ ምዌብሳ ፍራንሲስ በበኩላቸው የኡጋንዳን የንግድና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ለማጠናከር የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ተሞክሮ የተሻለ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም ከምክር ቤቱ ጋር ተቀራርቦ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡


የሁለቱ ሀገራት የንግድ ምክር ቤቶችም ተቀራርቦ በመስራት የሀገራቱ ቢዝነሶች በጋራ ተጠቃሚ የሚሆኑባቸውን አማራጮች ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባም በውይይቱ ተነስቷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...