• በቀጣዩ ዓመት 1.28 ትሪሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል
በ2017 በጀት ዓመት 900 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የእቅዱን 100 በመቶ ማሳካቱን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።
የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት እየተገመገመ ነው።
በግምገማው የበጀት ዓመቱ ሀገራዊ ተልዕኮ በአግባቡ የተከወነበት፣ የገቢውን ሥርዓት የሚፈትኑ ተግዳሮቶችን ለማቃናትና ሕግ ለማስከበር የተሰራበት መሆኑ ተብራርቷል።
ይህን በማጠናከርም በ2018 በጀት ዓመት 1 ነጥብ 28 ትሪሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱ ነው የተገለፀው።
