ከሰባት የሀይማኖት ተቋማት የተወከሉና ከእያንዳንዱ የሀይማኖት ተቋም ሶስት ሶስት ተወካዮች በጠቅላላው 21 የሀይማኖት አባቶች በዛሬው ዕለት ወደ ትግራይ ክልል መቀሌ ማምራታቸውን ምንጮቻችን ገልፀዋል።
በቆይታቸውም ከፕሬዝዳንት ታደሰ ወረዳ እንዲሁም ከሰራዊቱ አዛዦች ጋር በሰላም ዙሪያ ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ/ዶ/ር/ ጦርነት ከተጀመረ በኋላ መናገር ትርጉም ስለሌለው ጦርነቱ ሳይጀመር የሀይማኖት አባቶች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ሽማግሌዎች ወደ ትግራይ ክልል በመሄድ ስራቸውን እንዲሰሩና እንዲያሸማግሉ ለፓርላማው መናገራቸውን አይዘነጋም።
ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም የተቀሰቀሰው ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ተመሳሳይ የሽምግልና ሂደት ተደርጎ የነበረ ቢሆንም አለመሳካቱና ወደ ጦርነት መገባቱ የሚታወስ ነው።
