የሃይማኖት አባቶች ለሽምግልና ወደ መቀለ አቀኑ

Date:

ከሰባት የሀይማኖት ተቋማት የተወከሉና ከእያንዳንዱ የሀይማኖት ተቋም ሶስት ሶስት ተወካዮች በጠቅላላው 21 የሀይማኖት አባቶች በዛሬው ዕለት ወደ ትግራይ ክልል መቀሌ ማምራታቸውን ምንጮቻችን ገልፀዋል።


በቆይታቸውም ከፕሬዝዳንት ታደሰ ወረዳ እንዲሁም ከሰራዊቱ አዛዦች ጋር በሰላም ዙሪያ ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ/ዶ/ር/ ጦርነት ከተጀመረ በኋላ መናገር ትርጉም ስለሌለው ጦርነቱ ሳይጀመር የሀይማኖት አባቶች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ሽማግሌዎች ወደ ትግራይ ክልል በመሄድ ስራቸውን እንዲሰሩና እንዲያሸማግሉ ለፓርላማው መናገራቸውን አይዘነጋም።

ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም የተቀሰቀሰው ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ተመሳሳይ የሽምግልና ሂደት ተደርጎ የነበረ ቢሆንም አለመሳካቱና ወደ ጦርነት መገባቱ የሚታወስ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...