ህንዳዊ ዜግነት ያላቸው ግለሰብ አስክሬናቸው በአዳማ ፖሊስ መገኘቱን በኢትዮጵያ የህንድ ኢንባሲ አስታወቀ።
ህንዳዊ ዜግነት ያለው እና በአዳማ አከባቢ ቢሮውን ባደረገው በካልፓታሩ ፕሮጀክት ኢንተርናሽናል ሊሚትድ በተሰኘ ተቋም (KPIL) ሲሰራ የነበረ ግለሰብ በአዳማ አከባቢ ሞቶ መገኘቱን በኢትዮጵያ የሚገኘው የህንድ ኤምባሲ አስታውቋል።
ኤምባሲው ባወጣው አጭር መግለጫ ናቭ ሱቫሪዮ የተሰኙትና በአዳማ-አዋሽ ፈጣን መንገድ ፕሮጀክት ላይ የተቋሙ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ግለሰብ፥ ” አስክሬናቸው በአዳማ ፖሊስ የተገኘ ሲሆን የሞቱን ትክክለኛ መንስኤ ለማጣራት ምርመራ እየተካሄደ ነው ” ሲል አስታውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለ ጉዳዩ ለማጣራት ወደ ሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ቢያደርግም ለጊዜው ምላሽ ማግኘት አልቻለም።
@tikvahethiopia
