የቋንቋ እና የባህል እድገት ጉዳይ የሲቪል ማኅበራት ይሁን

Date:

መንግስት ለባህል እድገት እና ልማት የሚመድበውን በጀት አቋርጦ ጉዳዩን ለሲቪል ማኅበራት እንዲተው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ጠይቋል።

“ከግብር ከፋዩ የሚሰበሰብ የህዝብ ሀብት ለአጠቃላይ ሐገራዊ ልማበት ብቻ መዋል አለበት” ያሉት የፓርቲው የስራ አስፈጻሚ አባል አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን፣ እንደተናገሩት “መንግስት ከብሔር ቋንቋና ባህል ድጋፍ መዋቅር ሙሉ በሙሉ መውጣት አለበት”

የኢዜማ ስራ አስፈጻሚ አባል አርክቴክት ዮሐንስ አክለውም፤ “ማንነት የማኅበረሰብ እሴት እንጂ የፖለቲካ ጉዳይ አይደለም” ብለዋል፡፡  

የቋንቋና የባህል ዕድገት በሲቪል ማኅበራት መመራት እንደሚኖርበት እና የሕብረተሰብ ክፍሎች የራሳቸውን እሴት በራሳቸው መዋጮ መጠበቅ አለባቸው ሲሉ አስረድተዋል።

መንግስት ከማንነትና ከሃይማኖት ጉዳዮች መውጣት እንዳለበት ያሳሰቡት አቶ ዮሐንስ ትኩረቱን በጋራ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ብቻ ማድረግ ይገባዋል ብለዋል።

የታክስ ከፋዩን ሀብት ለተወሰኑ ቡድኖች ፍላጎት ማዋል አድሏዊ አሠራርን ይፈጥራል። ይህ ደግሞ በሀገሪቱ ግጭትን የመፍጠር አቅም አለው ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ከአሐዱ ራዲዮ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ለአባታቸው ግድያ “የበቀል እርምጃ” እንደሚወሰድ ተናገሩ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ በጽሑፍ ባስተላለፉት መልዕክት አባታቸው...

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል

ቡድኑ ነገ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አለመጠየቋን አስታወቀች

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፤ አገራቸው...

ሱዳን ዉስጥ ለሦስት ዓመታት የተካሄደው ጦርነትን ሰለ ማቆም

የሱዳን ብሔራዊ ጦር ለሦስት ዓመታት የተካሔደውን ጦርነት ለማቆም አሜሪካ...