በደራሲ አበረ ሽፈራው የተፃፈው “የበርበሬ ዐውሎ ነፋስ” የተሰኝው አዲስ መፅሐፍ ዋልያ መጽሐፍት አዳራሽ በርካታ ታዳሚያን በተገኙበት በድምቀት ተመረቀ ::
በዚህ የመጽሐፍ ምርቃት ፕሮግራም ላይ ሰለሞን ሳህለ፣ ቢንያም ውብሸት ፣ ኤደን ሃብታሙ ፣ እናኑ ግርማ ፣ ህይወት እምሻው ከመጽሐፉ ላይ በንባብ እቅቅርበዋል:: ደራሲ አበረ ሽፈራው በአዲስ ልሳን ጋዜጣ እና በፉና በጋዜጠኝነት አገልግሏል::
የእለቱ የክብር እንግዳ በመሆን መጽሐፉን በይፋ የመረቁት የመጽሐፉ ደራሲ አበረ ሽፈራው ወላጅ አባት እና የአበረ የትዳር አጋር የሆነችው የደራሲ ህይውት እምሻው እናት ነበሩ:: የደራሲው ወላጅ አባት በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ እንደተናገሩት :-
” ከልጅነቱ ጀምሮ መጽሐፍ ማንበብብ ይወድ ስለነበር እኔም በወር እስከ ሶስት መጵሐፍትን እየገዛሁ እንዲያነብ አደርግ ነበር::
ዛሬ እርሱም መጽሐፍ ጽፎ የእርሱን መጽሐፍ ለመመረቅ ስለበቃሁ በጣም ደስ ብሎኛል::
እንክዋ ደስ ያለህ ” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል::ደራሲውም ለአባቱ የአክብሮትና የምስጋና ሥጦታ አበርክቷል::
(ይትባረክ ዋለልኝ)
