የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ 12 ኛ ዓመት በዓለ ሢመት ተከብሮ ዋለ!

Date:

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት 12ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በዛሬው ዕለት ተከብሮ ውሏል።

በበዓሉ ላይ ያሬዳዊ ዝማሬዎች ፣ ቅኔ እና ሌሎች መርሐግብሮች የቀረቡ ሲሆን ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህርዳርና ሰሜን ጎጃም ሊቀ ጳጳስ ለቅዱስነታቸው የእንኳን አደረስዎ መልእክት አስተላልፈዋል።

በበዓሉ ላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የመምሪያ ኃላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች እና የውጭ ሀገር አምባሳደሮችና ተወካዮች እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ተገኝተዋል።

በመጨረሻም ቅዱስነታቸው አባታዊ መልዕክትና ቃለ ምዕዳን አስተላልፈው የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል፡፡

ቅዱስነታቸው የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም በተካሄደው በዓለ ሲመት በቃለ መሐላ ሐዋርያዊ ኃላፊነት የተረከቡ ሲሆን ፤ በርካታ መንፈሳዊ እና ሀገራዊ ተግባራትን እንዲሁም ሐዋርያዊ ጉዞዎችን እያከናወኑ ይገኛል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...