የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ በዘጠኝ ወራት 5.2 ቢሊዮን ብር ዓረቦን ሰበሰበ

Date:

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከአባል የፋይናንስ ተቋማት 5.2 ቢሊዮን ብር ዓረቦን መሰብሰቡን አስታወቀ።

የፈንዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ደሳለኝ አምባው እንደገለጹት ይህ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ11.10 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።

ከተሰበሰበው ዓረቦን ውስጥ 2.67 ቢሊዮን ብር (51.3%) ከግል ባንኮች፣ 2.47 ቢሊዮን ብር (47.5%) ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲሁም 59.49 ሚሊዮን ብር (1.2%) ከማይክሮፋይናንስ ተቋማት የተገኘ ነው።

በተጨማሪም ከጠቅላላው የፈንዱ ኢንቨስትመንት ውስጥ 11.17 ቢሊዮን ብር (92.24%) በመንግስት ግምጃ ቤት ሰነድ ላይ ኢንቨስት ተደርጓል።

የገንዘብ መድን ፈንድ ስራውን ከጀመረ ሁለት አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ነው። ዋና አላማው በባንክና በማይክሮፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ተቀማጭ ገንዘብ ላስቀመጡ ግለሰቦችና ድርጅቶች የመድን ሽፋን መስጠት ነው።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...