የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ በዘጠኝ ወራት 5.2 ቢሊዮን ብር ዓረቦን ሰበሰበ

Date:

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከአባል የፋይናንስ ተቋማት 5.2 ቢሊዮን ብር ዓረቦን መሰብሰቡን አስታወቀ።

የፈንዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ደሳለኝ አምባው እንደገለጹት ይህ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ11.10 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።

ከተሰበሰበው ዓረቦን ውስጥ 2.67 ቢሊዮን ብር (51.3%) ከግል ባንኮች፣ 2.47 ቢሊዮን ብር (47.5%) ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲሁም 59.49 ሚሊዮን ብር (1.2%) ከማይክሮፋይናንስ ተቋማት የተገኘ ነው።

በተጨማሪም ከጠቅላላው የፈንዱ ኢንቨስትመንት ውስጥ 11.17 ቢሊዮን ብር (92.24%) በመንግስት ግምጃ ቤት ሰነድ ላይ ኢንቨስት ተደርጓል።

የገንዘብ መድን ፈንድ ስራውን ከጀመረ ሁለት አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ነው። ዋና አላማው በባንክና በማይክሮፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ተቀማጭ ገንዘብ ላስቀመጡ ግለሰቦችና ድርጅቶች የመድን ሽፋን መስጠት ነው።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሰላም ስምምነት ሳይፈጸም የንግድ መርከቦች ጉዞ እንደማይጀምሩ የነዳጅ ጫኝ ኩባንያ ኃላፊ ተናገሩ

የሲውዲን ነዳጅ አጓጓዥ ኩባንያ የሆነው ‘ስቴና በልክ’ ዋና ስራ...

የታሪካዊው ቁልቢ ገብርኤል የዕድሳት ጥሪ ፦ የ134 ሚሊዮን ብር ግዙፍ ፕሮጀክት

! ከተገነባ 64 ዓመታትን ያስቆጠረውና በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ምዕመናን የሚሳለሙት...

መርስክ የበርበራ ወደብ የጭነት አገልግሎቶችን ለጊዜው አቋረጠ

የዓለማችን ግዙፍ የመርከብ ድርጅት የሆነው መርስክ ፣ ወደ በርበራ...

የምርጫ ካርድ፡ የአገር ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ

ግዮን መጽሔት :- በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዞ ውስጥ ምርጫዎች የሥልጣን...