የትራምፕና ዘለንስኪ ውይይት

Date:


የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ሊወያዩ መሆኑ ተሰምቷል። ዘለንስኪ ለዚሁ ውይይት ወደ በርሊን ያቀናሉ የተባለ ሲሆን ከትራምፕ ጋር ሰፋ ያለ የቪዲዮ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ትራምፕ ከዘለንስኪ ባሻገር ሌሎች የአውሮፓ ሀገራት መሪዎች ጋር በኦንላይን ውይይት ያደርጋሉም ተብሏል።

ውይይቱ በዋነኝነት ትራምፕ በመጪው አርብ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ሲገናኙ የዩክሬንን ፍላጎት ያማከለ ስምምነት እንዲያደርጉ ለመምከር መሆኑም ተሰምቷል።

የጀርመኑ ቻንስለር ፍሬድሪክ ሜርዝ ለዚሁ የቪድዮ ስብሰባ ዘለንስኪን ጨምሮ እንግሊዝ ፤ፈረንሳይ፤ የአውሮፓ ህብረት አመራሮችን ወደ በርሊን ጠርተዋልም ተብሏል።

ትራምፕ ፑቲንን በመጪው አርብ በአላስካ ከማግኘታቸው አስቀድሞ የሚደረገው ይህ የቪድ ስብሰባ ላይ የትርምፕ ምክትል ጄዲ ቫንስ ተሳታፊ ይናሉ ተብሏል።

የመጪው አርብ የዶናልድ ትራምፕና የፑቲን በአካል መገናኘት የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜም ያርገዋል።በዚህም ኬቭ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ መግባቷ ተሰምቷል።

ዘገባው የፍራንስ 24 ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...

የእግር ኳስ ዳኝነት በኢትዮጵያ

ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ግዮን መጽሔት :- እግር ኳስ...

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...