በእስራኤል ታሪክ የመጀመሪያው ጥቁር ኢትዮጵያዊ ፕሮፌሰር!

Date:

ፕሮፌሰር አንበሰ ተፈራ ትውልድና ዕድገታቸው በኢትዮጵያ ሲዳማ ክልል ቦርቻ ወረዳ ነው። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሥነልሳን (Linguistics) አግኝተዋል። በዩኒቨርስቲው በመምህርነት ሙያም አገልግለዋል።

ፕሮፌሰሩ እ.ኤ.አ በ1989 ወደ እሥራኤል ሀገር በማቅናት የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከኽብሪው ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል፡፡ በእስራኤል ሀገር  በኽብሪውና በተል አቭቪ ዩኒቨርስቲ ከ15 ዓመታት በላይ በመምህርነት አገልግለዋል።

በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው በዕብራይስጥ ባህልና ቋንቋ ጥናት፣ በአረብኛ፣ በአማርኛና በሲዳማ ቋንቋ ጥናት ፈር ቀዳጅ መምህርና ተመራማሪም ናቸው። ከዚህም ባሻገር በእስራኤል ትምህርት ሚኒስቴር የአማርኛ ቋንቋ ትምህርትና ጥናት አማካሪ በመሆንም ያገለገሉ ታላቅ የቋንቋ ልሂቅ ናቸው።

ፕሮፌሰር አንበሰ ተፈራ በአካዳሚክ ዓለም ቆይታቸው ከ20 በላይ የምርምር ጽሑፎችን አሳትመዋል። ሦስት መጽሐፍት ጽፈል። የሲዳምኛ ሙሉ ሥነልሳን ከዛሬ 25 ዓመት በፊት በማጥናት ለሲዳሙ አፎ እድገት ሳይንሳዊ መሠረት የጣሉ የሲዳማ ህዝብ የምንጊዜም ባለውለታ ናቸው።

እኚህ የቋንቋ (የሥነልሳን) ተመራማሪ፣ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከተቀበሉ ከ15 ዓመታት በኋላ በማግኘት፣ በእስራኤል ሀገር ታሪክ የመጀመሪያው ጥቁር፣ የመጀመሪያው  ኢትዮጵያዊ ሆነዋል፡፡

ፕሮፌሰሩ ከበርካታ ዓመታት በኋላ ወደ  ትውልድ መንደራቸው ሲመጡ ታላቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...