የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአነስተኛ አርሶ አደሮች የሚቀርብ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ

Date:

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በክልሉ ለሚገኙ ባለአነስተኛ ይዞታ አርሶ አደሮች የግብርና ብድር አቅርቦት ለማስጀመር የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ።

ስምምነቱ በጦርነት ክፉኛ የተጎዳውን የክልሉን ግብርና ለማነቃቃትና አርሶ አደሩን የፋይናንስ ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ባንኩ አስታውቋል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተና ጀነራል ታደሰ ወረደ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ ባንኩ ለአርሶ አደሩ ያዘጋጀው የብድር አቅርቦት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም “ከገበሬው የሚጠበቀው ምርታማነት ፍሬ እንዲያፈራ የፋይናንስ አቅርቦቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተግባራዊ መሆን አለበት” ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሰሜን ሪጅን ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሳሙኤል ተስፋሁነኝ በበኩላቸው፣ ባንኩ የፋይናንስ አካታችነትን ለማሳደግና አርሶ አደሩ በሀገራዊ ኢኮኖሚ ውስጥ የራሱን ሚና እንዲጫወት ለማስቻል እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩም አርሶ አደሮች የብድሩ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከባንኩ ጋር በቅርበት እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል።

የባንኩ የመቐለ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ልሳነወርቅ፣ የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

የብድር አቅርቦቱ በተለይ በትንንሽ እርሻዎች ላይ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች ቀጥተኛ የፋይናንስ ድጋፍ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

ይህ ስምምነት በትግራይ ክልል የተጀመረውን የመልሶ ማቋቋም ጥረት የሚያግዝ ሲሆን፣ አርሶ አደሮች ዘመናዊ የግብርና ግብዓቶችን እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...