የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን 254 ነዳጅ ጫኝ ቦቴዎችን በ116 ሚሊዮን ብር ቀጣ

Date:



የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን መዳረሻቸውን በማዘግየት እና ያልተገባ ትርፍ ለማግኘት የነዳጅ ስርጭት ችግር የፈጠሩ 254 ነዳጅ ጫኝ ቦቴዎች ላይ የ116 ሚሊዮን ብር ቅጣት እንደጣለ አስታወቀ። በተጨማሪም 354 የነዳጅ ማደያዎች ላይ በክልሎች በኩል ክስ እንደተመሰረተባቸው ገልጿል።

የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ደስታው መኳንንት እንደተናገሩት፣ አንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች የተቀበሉትን ነዳጅ በወጣላቸው የዋጋ ተመን መሸጥ ሲገባቸው፣ ዋጋ ጨምረው በህገወጥ መንገድ ይሸጣሉ። የዋጋ ማስተካከያ ተደርጎ ጭማሪ ይኖራል በሚል ግምትም ነዳጅ በመደበቅ የችግር መንስኤዎች ናቸው።

ከዲጂታል ሽያጭ ውጪ በእጅ በእጅ ሽያጭ ባከናወኑ 526 ማደያዎች ላይ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የተሰጠ ሲሆን፣ ከድርጊታቸው ያልታቀቡት 354 ማደያዎች ላይ ደግሞ በክልሎች በኩል ክስ ተመስርቶ በሂደት ላይ ይገኛል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...