የአሜሪካ ጦር ኃይሎችን የረዱ አፍጋኒስታናውያን ወደ ሀገራቸው ሊመለሱ ነው

Date:

የትራምፕ አስተዳደር ከአሜሪካ ኃይሎች ጋር አብረው የሠሩ አፍጋኒስታናውያን ወደ አሜሪካ እንዲዛወሩ የረዳውን ቁልፍ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢሮ እያፈረሱ ነው ሲል ዘ ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል፡፡

በአሜሪካ የአፍጋኒስታን ቆይታ ወቅት በአስተርጓሚነት፣ ሾፌርነት እና የሲቪል ሠራተኞች ሆነው ያገለገሉትን አብዛኞቹን ጨምሮ ከ250 ሺህ በላይ አፍጋኒስታናውያን በአሁኑ ጊዜ በእንጥልጥል ላይ ይገኛሉ፡፡

በኳታር፣ ፓኪስታን እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በሚገኙ ካምፖች ውስጥ እንዲቆዩ የተደረጉ አንዳንዶች ደግሞ ታሊባን ወደሚመራት አፍጋኒስታን በግዴታ የመመለስ አደጋ አንዣቦባቸዋል፡፡

የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፤ አሜሪካ የስደተኞች ማመልከቻ ሂደትን እያዘገየች እና የሎጂስቲክስ ድጋፍ እያቋረጠች መሆኑን ተከትሎ ከአፍጋኒስታን እንዲወጡ የተደረጉ ሰዎችን ወደነበሩበት መመለስ መጀመሯን ለዘ ዋሽንግተን ፖስት የደረሰው መረጃ ያሳያል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...