የአርሰናሉ ተጫዋች በሚቀጥለው ሳምንት የኢትዮጵያን ምድር ይረግጣል

Date:

የቀድሞ የአርሰናልና የማን.ሲቲ እንደዚሁም የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የነበረው ባካሪ ሳኛ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው።

የቀድሞው የአርሰናል እና የማንችስተር ሲቲ የመስመር ተከላካይ ባካሪ ሳኛ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ልምዱን እንደሚያካፍል ነው የተነገረው።

ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከአለም አቀፍ ተቋሞች ጋር ግንኙነት እንዲፈጠር እየሰራ የሚገኘው ዮሀንስ ዘውዱ ወይንም በተለምዶ ጆኒ ቬጋስ አማካኝነት ነው ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣው ተብሏል።

ኢትዮጵያዊው የእግርኳስ ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣም ይፋ አድርጓል።

ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣም ከአርሰናል ደጋፊዎች ጋር ይገናኛል የአርሰናል ኦርጅናል ማለያም ያበረክታል ብሏል።

ባካሪ ሳኛ በኢትዮጵያ የሚያደርገው ቆይታ ለምን ያህል ቀን እንደሆነ አልተገለጸም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...