የአርሰናሉ ተጫዋች በሚቀጥለው ሳምንት የኢትዮጵያን ምድር ይረግጣል

Date:

የቀድሞ የአርሰናልና የማን.ሲቲ እንደዚሁም የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የነበረው ባካሪ ሳኛ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው።

የቀድሞው የአርሰናል እና የማንችስተር ሲቲ የመስመር ተከላካይ ባካሪ ሳኛ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ልምዱን እንደሚያካፍል ነው የተነገረው።

ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከአለም አቀፍ ተቋሞች ጋር ግንኙነት እንዲፈጠር እየሰራ የሚገኘው ዮሀንስ ዘውዱ ወይንም በተለምዶ ጆኒ ቬጋስ አማካኝነት ነው ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣው ተብሏል።

ኢትዮጵያዊው የእግርኳስ ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣም ይፋ አድርጓል።

ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣም ከአርሰናል ደጋፊዎች ጋር ይገናኛል የአርሰናል ኦርጅናል ማለያም ያበረክታል ብሏል።

ባካሪ ሳኛ በኢትዮጵያ የሚያደርገው ቆይታ ለምን ያህል ቀን እንደሆነ አልተገለጸም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...