የአዲስ አበባ መታወቂያ የአገልግሎት ዘመን እና ሌሎች ማሻሻያዎች ሊደረጉለት  ነው

Date:

የከተማዋ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ እንዳስታወቀው በቀጣይ ወራት በስራ ላይ ያለውን  የነዋሪነት መታወቂያ ይዘት፣ የአገልግሎት ዘመን እና የገፅ ዲዛይን ከተማዋ ያለችበትን ደረጃ በሚመጥን እና ፋይዳን መሰረት ባደረገ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ አገልግሎት የሚሰጥ /  Smart  Card/  አድርጎ ለማሻሻል ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝም አስታውቋል።

በተጨማሪም  ተቋሙ ለ 2 ሚሊዮን ነዋሪዎች የዲጂታል ካርድ መታወቂያን  መሰጠቱን ገልፆል።

ይህ የመታወቂያ የዲጂታል ምዝገባ የነዋሪን የባዮሜትሪክ መረጃን ያካተተ  እና ከ35 በላይ  ለማስረጃነት ጥቅም ላይ የሚውሉ የግለሰብ መረጃዎች  የሚመዘገቡበት ስርዓት መሆኑን ኢትዮ ኤፍኤም ከተቋሙ ያገኘው መረጃ  ይጠቁማል።

የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የወረቀት መታወቂያ መስጠትን ለመጨረሻ ግዜ ማብቃቱን እና  ሙሉ ለሙሉ ወደ ዲጂታል ሽግግር መደረጉን  ባለፈው ሰኔ 25/2016ዓ.ም ይፋ ማድረጉን በመረጃው  አስታውሷል።

በተቋሙ የወሳኝ ኩነት ምዘገባን ጨምሮ በጠቅላላው ወደ 3 ሚልዮን የሚጠጉ ነዋሪዎች መረጃ በዲጂታል ምዘገባ የመረጃ ቋት ውስጥ እንዳለም አመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...