የኢራንና ሳውዲ ግንኙነት

Date:

የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ሳውዲ አረቢያ ገብተዋል፡፡

ከሳውዲው ልዑል መሐመድ ቢን ሳልማን (ኤም ቢ ኤስ) ጋር  በጅዳ ውጤታማ ዲፕሎማሲያዊ ውይይት ማድረጋቸውም ተሰምቷል።

ሰይድ አባስ አራግቺ ከ12 ቀናቱ ጦርነት በኋላ ወደ ሳውዲ አረቢያ ብቅ ሲሉ የመጀመሪያቸው ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

ቴህራን እና ሪያድ ዲፕሎማሲያው መንገዶችን እያጠናከሩ መሄዳቸውን የሚጠቁም ጉዞ ተደርጎ ሲወሰድ፣ አገራቱ ቻይና ካሸማገለቻቸው ወዲህ በመካከለኛው ምስራቅ ፖለቲካ ውስጥ ሚናቸውን የጋር እያደረጉት እንደሆነ ያሳያልም ተብሏል።

ስለአሁናዊ የቀጠናው ሁኔታዎች እና ስለተፈጠሩ አዳዲስ ነገሮች የተወያዩ ሲሆን፣ ልዑሉ እና አራግቺ የተሰሩ ስራዎችንም ገምግመዋል።

ውጥረቶችን ለማብረድ የተደረሰው ስምምነት ለሰላም እና መረጋጋት ትልቅ ሚና እንዳለው መሐመድ ቢን ሳልማን ተናግረዋል።

ሳውዱ አረቢያም በመካከለኛው ምስራቅ ሰላማዊ የዲፕሎማሲ መንገዶችን እንደምትከተል ከመወሳቱ ባሻገር፣ የቀጠናው መረጋጋት ለሁለንተናዊ እንቅስቃሴና ዕድገት ቁልፍ ሚና እንደሚኖረውም ታሳቢ ተደርጓል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...