የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት የኬብል አምራቹን ድርጅት ጎበኙ

Date:

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶ/ር እመቤት መለሰና የባንኩ የአመራር አባላት፣ በሰበታ ከተማ የሚገኘውን የቢሜት የኢነርጂና ቴሌኮም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማሕበርን ጎበኙ፡፡

የባንኩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር እመቤት መለሰ ከጉብኝቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት፤ ድርጅቱ ከፍተኛ አቅም የፈጠረና እንደ ሀገርም ለሚካሄደው የኢኮኖሚ ሽግግር ከፍተኛ አስተዋጽ የሚያደርግ ሥራ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የጉብኝቱም ዓላማ ድርጅቱ ያለበትን አሁናዊ አቋም በመገምገም፣ በቀጣይ ከባንኩ ጋር ያለውን ግንኙነት ጤናማና ውጤታማ ማድረግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ለመወያየት እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታደሰ አድማሱ በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የገንዘብና ቴክኒክ ድጋፍ የተቋቋመው ቢሜት ኬብል ማምረቻ፣ በሀገራችን ከሚገኙ ኬብል አምራች ኩባንያዎች አንዱና ዋነኛው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ሥራ አስፈጻሚው የቢሜት የኢነርጂና ቴሌኮም፣ ለትልልቅ ግንባታዎችና መሠረተ ልማት የኤሌክትሪክና ኮምዩኒኬሽንስ ኬብሎችን የሚያቀርብ መሆኑን ጠቅሰው፣ እንደሀገር በተጀመረው የማክሮ ኢኮኖሚ ግንባታ የበኩሉን ሚና እየተወጣ ነው ብለዋል፡፡

በቀጣይም ይህንን ሀገራዊ ፋይዳ ያለውን ድርጅት የበለጠ አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ለማስቻል ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በሚኖረው ግንኙነት ላይ ውይይት ማድረግና በጋራ መሥራት እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...