የኢትዮ ቴሌኮምና የዜድ ቲ ኢ ግዙፍ የኔትወርክ ማስፋፊያ ስምምነት

Date:

በስፔን ባርሴሎና እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የሞባይል ዓለም አቀፍ ኮንግረስ ጎን ለጎን፣ ኢትዮ ቴሌኮም የኔትወርክ አቅሙን ለማዘመንና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት የሚያስችል ግዙፍ ስምምነት ከቻይናው ዜድ ቲ ኢ (ZTE) ኮርፖሬሽን ጋር ተፈራርሟል፡፡

በዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ፍሬሕይወት ታምሩ የተፈረመው ይህ ፕሮጀክት በአጠቃላይ 647 አዳዲስ የኔትወርክ ጣቢያዎችን መገንባትን የሚያካትት ሲሆን፣ በዋናነትም ዘመናዊ የሞባይል ብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው የገጠር አካባቢዎች ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የሀገሪቱን የ4ጂ የሕዝብ ሽፋን ወደ 95.5 በመቶ በማሳደግ የአገልግሎት ጥራትን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሻሽል ይጠበቃል፡፡

ስምምነቱ የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ከማፋጠኑ ባለፈ፣ የዲጂታል ሥነ-ምህዳሩን በማዘመን ረገድ የላቀ ሚና ይጫወታል።

ይህ ስምምነት ኩባንያው ከኤሪክሰን ጋር ካደረገው ተመሳሳይ የቴክኖሎጂ አጋርነት ጋር ተዳምሮ የኢትዮጵያን የቴሌኮም መሠረተ ልማት ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ታምኖበታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...