“በየሳምንቱ አንድ ሚሊዮን ዜጎችን እየመዘገብኩ ነው”

Date:

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ፅሕፈት ቤት በየሳምንቱ አንድ ሚሊዮን ዜጎችን እየመዘገበ መሆኑን በማብሰር፣ እስካሁን የተመዝጋቢዎች ቁጥር 37.5 ሚሊዮን መድረሱን አስታውቋል።

የፅሕፈት ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሄ አርአያስላሴ እንደገለጹት፤ እስከ መጪው ሰኔ ወር ድረስ ተመዝጋቢዎችን 90 ሚሊዮን ለማድረስ ግብ ተቀምጦ እየተሰራ ይገኛል።

ይህ ዲጂታል መታወቂያ ለማንነት ማጭበርበር መከላከያነት ከመዋሉ ባለፈ፣ በሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት (GDP) ላይ የ6 በመቶ እድገት እንደሚያስገኝ ይጠበቃል።

መታወቂያው ለባንክና ቴሌኮም አገልግሎቶች፣ ለግብር ከፋይ መለያ (TIN) እና ለተማሪዎች ምዝገባ እንደ ቅድመ-ሁኔታ የሚያገለግል ሲሆን፣ ስደተኞችም የሀገሪቱን አገልግሎቶች እንዲያገኙ ያስችላል።

ምንም እንኳን የክትትል ስጋት ያላቸው ወገኖች ቢኖሩም፣ ፕሮግራሙ ግልጽነትን በመፍጠር የመልካም አስተዳደርና የደህንነት ስራዎችን ለማቀላጠፍ ያለመ ነው።

ለዚህም ስኬታማነት የመገናኛ ብዙኃን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሚና ወሳኝ መሆኑ በፕሮግራሙ ላይ ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...