በኢትዮጵያ እንደ ዓለም አቀፍ የኦንላይን የገበያ መሪዎች ለመሆን የጀመረው “ኑግዙ” የተሰኘው አዲስ የኢ-ኮሜርስ መድረክ መጀመሩ ለሀገሪቱ የዲጂታል ንግድ ትልቅ ተስፋን ሰንቋል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን የገበያ ሁኔታ በጥንቃቄ መገምገም ኑግዙ እና በአጠቃላይ የኢ-ኮሜርስ ዘርፉ የሰፋ ስኬት ለማግኘት በርካታ መሰናክሎችን ማለፍ እንደሚጠበቅባቸው የዘርፉ ባለሙያዎች አስገንዝበዋል።
በቅርቡ ሥራው የጀመረዉ ኑግዙ የተለያዩ ምርቶችን በማቅረብ ከመላ አገሪቱ ላሉ ሸማቾች ከአስመጪዎች አንስቶ እስከ አነስተኛ ነጋዴዎች ድረስ በቀላሉ እንዲገናኙ ዕድል ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የችርቻሮ ንግድን ዘመናዊ ለማድረግ የሚደረግ አበረታች እርምጃ ቢሆንም፣ ወደ ስኬት የሚወስደው መንገድ በዋናነት በመሠረተ ልማት፣ በፋይናንስ እና በባህላዊ አስተሳሰብ የተሞሉ ተግዳሮቶች እንደሚበዙበት በዘርፉ ከ 15 ዓመታት በላይ የቆየዉና የኢኮኖሚክስ ባለሙያ እና አማካሪ የሆኑት ዘላለም ከፍያለሁ ( ዶ/ር) ተናግረዋል።
CapitalNews
