የኤርትራዉ ቃል አቀባይ የማነ ገብረመስቀል ምን አሉ?

Date:

የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገብረመስቀል፣ መቀመጫውን ዋሽንግተን ያደረገው “ዘ ሴንትሪ” የተሠኘው መንግሥታዊ ያልኾነ ተቋም በኤርትራ ላይ ያወጣው ሪፖርት “የስም ማጥፋት ውንጀላ” ነው በማለት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሠፈሩት ጽሁፍ ውድቅ አድርገዋል።

የማነ፣ የተወሰኑ የተቋሙ የቦርድ አባላት፣ “በአደራዳሪነት ሽፋን የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ጦርነትን በማባባስ” የሚታወቁ፣ ለኢትዮጵያ መንግሥት ወግነው የነበሩና የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ላይ ማዕቀብ እንዲጥል ከፍተኛ ሚና የተጫወቱ ነበሩ በማለት ወቅሰዋል።

ተቋሙ “ሥልጣና እ ዝርፊያ፤ የኤርትራ ጦር ጣልቃ ገብነት በትግራይ‘’ በሚል ርዕስ ከቀናት በፊት ባወጣው ሪፖርት፣ ኤርትራ ሠራዊቷን እንደገና እያስታጠቀችና ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦቿም በትግራይ በሰዎች ዝውውር፣ በሰዎች እገታና በሕገወጥ የወርቅ ማዕድን ንግድ እንደሚሳተፉ ገልጦ ነበር። [ዋዜማ]

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...