የእስራኤል ጦር ጥቃቱን ማጠናቀቁን ሲገልጽ፣ ተመድ በአስቸኳይ ሊሰበሰብ ነው

Date:

በኢራን ላይ የተፈጸመው ጥቃት

የእስራኤል መከላከያ ኃይል “በኢራን አገዛዝ” ላይ አካሄድኩ ያለውን “መጠነ ሰፊ ጥቃት” ማጠናቀቁን ሲያስታውቅ፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ሊያደርግ ነው።

እስራኤል ከአሜሪካ ጋር በመቀናጀት ቅዳሜ ጠዋት በኢራን ላይ በከፈተችው ጥቃት “አንዱ ዒላማ የነበረው በምዕራባዊ ኢራን ኬርማንሻህ አካባቢ ያለው ዘመናዊ የአየር ጥቃት መከላከያ ሥርዓት” እንደነበረ የእስአኤል ጦር ገልጿል።

ጦሩ በመግለጫው የተፈጸሙት ጥቃቶች “የኢራን አብዮታዊ ዘብ አቅምን ለማዳካም እና በእስራኤል ላይ ሊፈጸሙ የሚችሉ ጥቃቶችን ለማምከን የእስራኤል አየር ኃይል በኢራን አየር ክልል ውስጥ የሚያካሂደውን ጥቃት ያለ እንቅፋት ለመፈጸም የሚሰስችል ነው” ብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የመንግሥታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ ቅዳሜ በኒው ዮርክ የሰዓት አቆጣጠር ከሰዓት በኋላ በተፈጸመው ወታደራዊ ጥቃት ላይ ለመነጋገር አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል።

ስብሰባው እንዲካሄድ የጠየቁት ባህሬን፣ ኮሎምቢያ፣ ቻይና፣ ሩሲያ እና ፈረንሳይ ሲሆኑ፣ የመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ቀደም ብለው “በመካከለኛው ምሥራቅ የታየውን ወታደራዊ ጥቃት” አውግዘዋል።

ዋና ፀሐፊው ባወጡት መግለጫ ወታደራዊ ጥቃቶቹ ዓለም አቀፍ ሰላምን እና ደኅንነትን የሚጎዱ በመሆናቸው “በአስቸኳይ እንዲቆሙ” ጠይቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...