የዓለም ጤና ድርጅት የዩኤስኤአይዲ ድጋፍ መቋረጥን ተከትሎ ቢያንስ ስምንት ሀገራት የኤች አይ ቪ መድኃኒት እጥረት ያጋጥማቸዋል ተባለ

Date:

ዩኤስኤ አይ ዲ በትራምፕ አስተዳደር አስተዳደር ውሳኔ መሰረት አብዛኛውን ስራው እንዲቋረጥ መደረጉን ተከትሎ በስምንት ሀገራት የነበረው የኤች አይ ቪ መድኃኒት አቅርቦት አደጋ ላይ ጥሎታል የተባለ ሲሆን ነገሩ በአፋጣኝ እልባት ካላገኘ በሀገራቱ የመድኃኒቱ አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ሊጠፋ ይችላል ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስጠንቅቋል።

ድርጅቱ እንደ ሄይቲ፣ ኬንያ፣ ሌሴቶ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ፣ ናይጄርያና ዩክሬን ያሉ ሀገራት በቀጣዮቹ ወራት በእጃቸው ላይ ያለውን የኤች አይ ቪ መድሓኒት እንደሚያልቅ ገልፆል። አክሎም ይህ መስተጓጎል ላለፉት 20 ዓመታት በኤች አይ ቪ ላይ የተሰራውን ስራ ወደ ኃላ የሚመልስ ነው ሲሉ የድርጅቱ ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር ቴድሮስ አድሓኖም ተደምጠዋል። ዳይኤክተሩ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ማብራሪያ ይህ መስተጓጎል በዓለም አቀፍ ደረጃ አዳዲስ 10 ሚሊየን የቫይረሱ ተጠቂዎችና ወደ 3 ሚልየን የሚጠጉ በቫይረሱ ሳብያ የሚሞቱ ሰዎች ይኖራሉ ብለዋል።

ከዚህ ባሻገር የትራምፕ አስተዳደር ውሳኔ ኤች አይ ቪ፣ ፖሊዮ፣ ወባና ቲቪ የመሳሰሉ በሽታዎችን ለመከላከል የሚደረጉ ጥረቶች የሚያስተጓጉል ነው ተብሎለታል። የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ጄነራሉ ዶ/ር ቴድሮስ አክለው አሜሪካ ቀጥተኛ የሆኑ ገንዘባዊ ድጋፎችን ለማቋረጥ ከወሰነች ሰብአዊና ስርዓት ባለው መንገድ ሀገራቱ ሌላ አማራጭ የመፍትሄ መንገድ የሚያገኙበት እድል የማመቻቸት ግዴታ አለባት ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የድጋፍ መቋረጡ በአፍጋኒስታን ከሚደረጉ የሰብአዊ ድጋፍና የጤና ነክ ስራዎች 80 በመቶዎቹ እንዲቋረጡ እንደሚያስገድድ የተገለፀ ሲሆን እእአ እስከ መጋቢት 4 ቀን ድረስ ባለው መረጃ መሰረት በዓለም አቀፍ ደረጃ 167 የጤና ተቋማት የተዘጉ ሲሆን አስቸኳይና አፋጣኝ የመፍትሄ እርምጃ ካልተወሰደም እስከ ሰኔ ድረስ ባለው ጊዜ ከ220 በላይ የጤና ተቋማት መዘጋታቸው አይቀሬ መሆኑ ተነግሯል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...