የዶ/ር ወዳጄነህ መልዕክት ምንድን ነዉ?

Date:

ለብፁዕ ቅዱስ አባታችን አቡነ ኤልያስ
የአርባ ምንጭ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ።

ብፁዕነትዎ በአባትነት ስልጣንዎ “ለዶ/ር ወዳጄነህ አድርሱልኝ” ብለው ያስተላለፉልኝ መልዕክት ደርሶኛል። ብዙ ሰዎች ቪዲዬውን እየላኩልኝ ደጋግሜ አየሁት፣ ሰማሁት።

በመጀመርያ የእኔ ከንቱ ስሞ በእርስዎ ቅዱስ አንደበት በመጠራቱ ብቻ እግዚአብሔርን አመሰግኛለሁ ። እርስዎ ለእኔ ብለው ተናገሩ፣ ጥሪ አቀረቡልኝ እንጂ ያለዚያማ የእኔ አይነቱ ሀጢያተኛ ወደ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቢመጣ ተጨማሪ ሸክም ቢሆንባት እንጂ እርሷን ምን ሊጠቅማት?

ብፁዕ አባታችን! እርስዎ ጥሪውን ያቀረቡበት የእግዚአብሔር ፍቅር ልብ የሚነካ ነበር። እንዲህ እንደርስዎ መለኮታዊ ፍቅር ያደረባችው አባቶች ቢበዙልን ምድራችን ትፈወስ ነበር ብዬ አምናለሁ። ያቀረቡልኝን ጥሪ፣ የመከሩኝን ምክር ስሜታዊ ሳልሆን ከልቤ፣ በፅሞና እንደማስብበት፣ እንደምፀልይበት ቃል እገባሎታለሁ።

እንግዲህ መልዕክትዎ ደጋግሞ ቢደርሰኝ ይቺን ትንሽ ፅሁፍ ልፅፍሎት ደፈርኩኝ።
ይቅር ይበሉኝ።

እግዚአብሔር ይስጥልኝ!
ውለታዎንም ይክፈልልኝ!

ዶ/ር ወዳጄነህ መሐረነ።

(ከዚህ ጋ በተገናኘም ባልተገናኘም መንገድ የተሳሳተ መረጃ የምታቀርቡ አንዳንድ ሚዲያዎች ብትታረሙ መልካም ይመስለኛል።

አንድ ሰው ታዋቂ ሆነ አልሆነ፣ ተማረ አልተማረ ወደ ቤተክርስትያን መምጣቱ፣ መመለሱ ጥቅሙ ለእሱው ነው እንጂ ለንፅህት፣ ቅድስት ቤተ ክርስትያን የሚጨምርላት አንዳች ነገር የለም።

“እከሌ ወደዚህ ተመለሰ” በሚል ያልተረጋገጠ ዜና እግዚአብሔር አይከብርም፣ ሀይማኖትም አይጠቀምም።)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...