የገንዘብ ሚኒስቴር ለሩብ ዓመቱ የ243 ቢሊዮን ብር የግምጃ ቤት ሰነዶች ጨረታ መርሃ ግብር ይፋ አደረገ

Date:

የገንዘብ ሚኒስቴር እ.ኤ.አ በ2025 የመጨረሻ ሩብ ዓመት የሚካሄደውን ጠንካራ የግምጃ ቤት ሰነዶች (T-Bills) የጨረታ መርሃ ግብር ይፋ ማድረጉን አስታውቋል።

ከመስከረም 21 እስከ ታኅሣሥ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄደው ይህ የሶስት ወራት መርሃ ግብር በአጠቃላይ 243.05 ቢሊዮን ብር የሚገመት የዕዳ ሰነድ ለሀገር ውስጥ ባለሀብቶች የሚያቀርብ ሲሆን። መንግሥት የሀገር ውስጥ የዕዳ ገበያን ለማጥለቅና ግልጽነትን ለማሳደግ በያዘው ቀጣይነት ባለው የፋይናንስ ማሻሻያ አጀንዳ ውስጥ ቁልፍ እርምጃ መሆኑ ተመላክቷል።

በተለይም ይህ የዕዳ ሰነድ አቅርቦት በየሁለት ሳምንቱ የሚካሄድ ሲሆን፣ ለባንኮች፣ ለኢንሹራንስ ኩባንያዎች፣ ለጡረታ ፈንድ እና ለሌሎች ተቋማት የተረጋጋ የኢንቨስትመንት ዕድልን ይፈጥራል።

ባለሀብቶች በአራት የተለያዩ የጊዜ ገደቦች ማለትም 28 ቀናት፣ 91 ቀናት፣ 182 ቀናትና 364 ቀናት ላይ መጫረት የሚችሉ ሲሆን፣ ይህም የኢንቨስትመንት ፖርትፎሊዮአቸውን በተለያየ መልኩ እንዲያስተዳድሩ ያስችላቸዋል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...