የጉምሩክ ኮሚሽን ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ውህደት ሚናዋን እንድትወጣ የበኩሉን ጥረት እያደረገ እንደሆነ ገለፀ

Date:



ይህ የተገለጸው ኢትዮጵያ እና ኬንያ የአንድ አለቅ የድንበር ጣቢያዎችን ለማስፋፋት የሚያስችል ውይይት ባካሄዱበት ወቅት ነው፡፡ ውይይቱ በጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ አሪና፣ የዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ተወካዮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል እንደተደረገ የኢትዮጵያ ጉሙሩክ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ከዓመታት በፊት አገልግሎት መስጠት የጀመረው የሞያሌ አንድ አለቅ የድንበር አገልግሎት ማዕከል ተደጋጋሚ ፍተሻዎችን በማስቀረት የተፋጠነ የጉምሩክ አገልግሎት እንዲኖር ማስቻሉን አንስተዋል፡፡

አክለውም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ውህደት ግንባር ቀደም ሚናዋን እንድትወጣ ኮሚሽኑ የበኩሉን ጥረት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ተጨማሪ የጋራ አንድ አለቅ የድንበር አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎችን ሱፍቱ እና ራሙ በሚባሉ የድንበር አካባቢዎች ለመገንባት ስለሚቻልበት ሁኔታም መክረዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...