የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በ6 ዙሮች እንደሚሰጥ ይታወቃል

Date:

ፈተናው እስካሁን ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በ3 ዙር በኦንላይን እና በወረቀት ከሰኔ 23/2018 ዓ/ም ጀምሮ ተሰጥቷል።

3ኛው ዙር የተፈጥሮ ሳንይስ ተማሪዎች ፈተና ከሐምሌ 1 እስከ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ተሰጥቶ ተጠናቋል።

በትግራይ ክልል ለሚገኙ ተማሪዎችም የኦንላይን ፈተናውን በአግባቡ መውሰዳቸው ፈተናውን ያስፈጸሙት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አሳውቀዋል።

በሀገር አቀፉ ፈተና 4ኛው ዙር የማኅበራዊ ሳይንስ ፈተና ከሰኞ ሐምሌ 6 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለ3 ተከታታይ ቀናት በወረቀት እና ኮምፒውተር ይሰጣል።

ፈተናው በ5ኛ እና 6ኛ ዙር እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ (በኮምፒዩተር) ቀጥሎ ፍጻሜውን ያገኛል።

በሌላ በኩል፣ በትግራይ ክልል ውስጥ በወረቀት ፈተናቸውን ላልተፈተኑ ተማሪዎች ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ይሰጣል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ለአባታቸው ግድያ “የበቀል እርምጃ” እንደሚወሰድ ተናገሩ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ በጽሑፍ ባስተላለፉት መልዕክት አባታቸው...

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል

ቡድኑ ነገ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አለመጠየቋን አስታወቀች

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፤ አገራቸው...

ሱዳን ዉስጥ ለሦስት ዓመታት የተካሄደው ጦርነትን ሰለ ማቆም

የሱዳን ብሔራዊ ጦር ለሦስት ዓመታት የተካሔደውን ጦርነት ለማቆም አሜሪካ...