የ90 መስሪያ ቤቶችን 271 ተሽከርካሪዎች በመሸጥ 322 ነጥብ 9 ሚልዮን ብር ተገኝቷል

Date:

በተያዘው በጀት ዓመት ግዢ እንዲፈጸምላቸው ላመለከቱ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎችና የፌዴራል ተቋማት ከ9 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት ለማቅረብ ጨረታውን ላሸነፉ ድርጅቶች የአሸናፊነት ደብዳቤ መሰጠቱን ያስታወቀው የመንግሥት ግዥ አገልግሎት ነው።


ተቋሙ ግዢውን የሚፈጽመው በ5 ዋና ዋና የንብረት መደቦች ማለትም በጽሕፈት መሣሪያዎች፣ በኮምፒውተር ቀለም ወይም ቶነሮች፣ በአይ.ሲ.ቲ መገልገያዎች፣ በጽዳት ዕቃዎችና በደንብ ልብሶች ላይ መሆኑ ታውቋል።

የአገልግሎቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ጎጃም ታደለ እንደገለጹት፣ ከተጠቃሚ መሥሪያ ቤቶች የተሟላ የመረጃ ፍላጎት ከተቀበሉ በኋላ የጨረታ ሂደት ተከናውኖ አሁን ላይ ለአቅራቢ ድርጅቶቹ የአሸናፊነት ደብዳቤ ተሰጥቷል።

በሌላ በኩል ተቋሙ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ የ90 መሥሪያ ቤቶችን 271 ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችና ልዩ ልዩ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድ 322 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመንግሥት ማስገኘቱን ሥራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።

በአጠቃላይ ለ178 የፌዴራል ተቋማት ግዢዎችን የመፈጸምና ያገለገሉ ንብረቶችን የማስወገድ ሥራዎችን የሚያከናውነው የመንግሥት ግዥ አገልግሎት፣ የዕቃዎች አቅርቦት ሂደቱ በተያዘለት ዕቅድ መሠረት እየተከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል።

አሐዱ ሬዲዮ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...