ጥቃቱ በኦዴሳ እና በኬርሶን ግዛቶች እንደሆነ ሲገለጽ ንጹሐንን ማዕከል ያደረገ መሆኑንም ኪዬቭ ገልጻለች፡፡
ማምሻውን በሩሲያ በደረሰው ጥቃትም አራት ሰዎች ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን ሰላሳ ያህል መቁሰላቸውም ተነግሯል፡፡
የሩሲያ የጦር አውሮፕላኖች በዩክሬን ኪዬቭ እና የተለያዩ ለ አካባቢዎች ጥቃት ማድረሳቸውንም የኪዬቭ ከንቲባ አረጋግጠዋል፡፡
የሩሲያ የመከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ 91 የዩክሬን የሰው አልባ ጦር አውሮፕላን ጥቃትን ማክሸፍ እንደቻለ ነው ያስታወቀው፡፡
ሚኒስቴሩ አክሎም በዲኒፕሮ ቀጣና ዳችኔ አካባቢን በቁጥጥሩ ስር እንዳዋለ አስታውቋል፡፡
ዘገባው የፍራንስ 24 ነው፡፡
