የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር በዲጂታል ማንነት ዙሪያ ባሳዩት የአመራርነት ብቃት ዓለም አቀፍ እውቅና አገኙ
ዋና መቀመጫውን በአሜሪካ ሳን ፍራንሲስኮ ያደረገው ኦክታ ኩባንያ የብሔራዊ መታወቂያ ዋና ዳይሬክተር ዮዳሔ አርአያስላሴን በዲጂታል ማንነት የአመራርነት ሚና ካላቸው 25 ሰዎች አንዱ አድርጎ እውቅና ሰጥቷቸዋል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም መርሐግብር ከ13 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተመዝግበዋል። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም እ.ኤ.አ በ2025 70 ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያንን ለመመዝገብ አቅዷል ሲል ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡
