Home ስፖርት ጆዜ ሞሪኒሆ ተቀጡ

ጆዜ ሞሪኒሆ ተቀጡ

ጆዜ ሞሪኒሆ ተቀጡ

በቱርክ ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ከጋላታሳራይ በነበራቸው ጨዋታ ያልተገባ ድርጊት የፈጸሙት አሰልጣኙ የ3 ጨዋታ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።

ፌነርባቼ 2 ለ 1 በተሸነፈበት ጨዋታ ፖርቹጋላዊው ጆዜ ሞሪኒሆ የጋላታሳራይ አሰልጣኝ የሆነውን ኦካን ቡሩክ አፍንጫ ይዘው በመጎተታቸው ነው ቅጣቱ የተጣለባቸው።

የቀድሞው የቼልሲ እና ማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ በተጨማሪም የ5 ሺህ 955 ፓውንድ የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።

ሁሌም ብጥብጥ በማያጣው የኢስታምቡል ደርቢ ፌነርባቼ 2 ለ 1 ተሸንፎ ከውድድር መሰናበቱ የሚታወስ ነው::

በዚህ ጨዋታ ላይ ሁለት የጋላታሳራይ እና አንድ የፌነርባቼ ተጫዋች ቀይ ካርድ መመልከታቸውም አይዘነጋም።