ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ኅብረት የሰው ሠራሽ አስተውህሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው ተሾሙ

Date:



ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአኅጉር ደረጃ ዘርፉን እንዲመሩ የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ሹመቱን እንደሰጣቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያ በዘርፉ እያሳየች ያለው ተሞክሮ እውቅና ማግኘቱ፣ በሀገሪቱ የተቋቋመው የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ኢንስቲትዩት እና የተቀረጸው ብሔራዊ ስትራቴጂ ውጤታማነት ተመራጭ እንዳደረጋቸው ፅ/ቤታቸው የሹመት ደብዳቤውን ጠቅሶ ገልጿል፡፡

አኅጉራዊው ሹመት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ነፃነት እና በክህሎት ልማት የምታደርገውን እንቅስቃሴ ለአፍሪካ አህጉር ተሞክሮ እንዲሆን ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርም ተመላክቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው የካቲት ወር የኅብረቱ የሰው ሠራሽ አስተውህሎትና ዲጂታል ጤና አምባሳደር ሆነው መሾማችው ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...