“የኒውክሌር ባለሙያዎች ከሌሉ ስምምነቱ አደገኛ ነው”

Date:



የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኃላፊ ካጃ ካላስ፣ በኢራን የኒውክሌር ድርድር ዙሪያ የዘርፉ ባለሙያዎች ካልተሳተፉ የሚደረገው ስምምነት “ደካማ” እና ለዓለም ሰላም አስጊ ሊሆን እንደሚችል አስጠነቀቁ።

በቆጵሮስ በተካሄደው የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች ጉባዔ ላይ እንደተገለጸው፣ የኒውክሌር ባለሙያዎች የሌሉበት ውይይት ኢራን ከዚህ ቀደም የነበሩትን ገደቦች እንድትጥስና ይበልጥ አደገኛ እንድትሆን ዕድል ሊሰጣት ይችላል።

በተለይም እ.ኤ.አ በ2015 የተደረገው ስምምነት ፈርሶ በነበረበት ሁኔታ፣ አዲሱ ድርድር ጥንቃቄ ካልተደረገበት ከበፊቱ የከፋ የደህንነት ስጋት ሊደቅን እንደሚችል ካላስ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ኃላፊዋ አክለውም፣ የኢራን የኒውክሌር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሚሳዔል ፕሮግራሞቿ፣ ለታጣቂ ቡድኖች የምታደርገው ድጋፍና በአውሮፓ ውስጥ የምታካሂዳቸው የበይነ-መረብ (Cyber) ጥቃቶች አብረው መፈታት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

እነዚህ ዘርፈ-ብዙ ችግሮች እልባት ካላገኙ፣ ኢራን በክልሉና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላት አስጊነት ይበልጥ አደገኛ እየሆነ እንደሚሄድ ተመልክቷል።

ማንኛውም ስምምነት የሀገሪቱን የኒውክሌር እንቅስቃሴ በትክክል መገደብና ዓለም አቀፍ ተቆጣጣሪዎች ወደ ቴህራን እንዲገቡ የሚያስችል ጠንካራ ማዕቀፍ ሊኖረው እንደሚገባም ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች”:-  ከዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል ጋራ ውይይት

ዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል በተለይ በ1997 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ 97...

የ12ኛ ክፍል የፈተና ቀን ታወቀ

የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሳልቫ ኬር ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት...

አሜሪካ ኤርትራ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ልታነሳ ነው !

የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ አሜሪካ ከኤርትራ ጋር ያላትን ግንኙነት...