የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኃላፊ ካጃ ካላስ፣ በኢራን የኒውክሌር ድርድር ዙሪያ የዘርፉ ባለሙያዎች ካልተሳተፉ የሚደረገው ስምምነት “ደካማ” እና ለዓለም ሰላም አስጊ ሊሆን እንደሚችል አስጠነቀቁ።
በቆጵሮስ በተካሄደው የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች ጉባዔ ላይ እንደተገለጸው፣ የኒውክሌር ባለሙያዎች የሌሉበት ውይይት ኢራን ከዚህ ቀደም የነበሩትን ገደቦች እንድትጥስና ይበልጥ አደገኛ እንድትሆን ዕድል ሊሰጣት ይችላል።
በተለይም እ.ኤ.አ በ2015 የተደረገው ስምምነት ፈርሶ በነበረበት ሁኔታ፣ አዲሱ ድርድር ጥንቃቄ ካልተደረገበት ከበፊቱ የከፋ የደህንነት ስጋት ሊደቅን እንደሚችል ካላስ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ኃላፊዋ አክለውም፣ የኢራን የኒውክሌር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሚሳዔል ፕሮግራሞቿ፣ ለታጣቂ ቡድኖች የምታደርገው ድጋፍና በአውሮፓ ውስጥ የምታካሂዳቸው የበይነ-መረብ (Cyber) ጥቃቶች አብረው መፈታት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
እነዚህ ዘርፈ-ብዙ ችግሮች እልባት ካላገኙ፣ ኢራን በክልሉና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላት አስጊነት ይበልጥ አደገኛ እየሆነ እንደሚሄድ ተመልክቷል።
ማንኛውም ስምምነት የሀገሪቱን የኒውክሌር እንቅስቃሴ በትክክል መገደብና ዓለም አቀፍ ተቆጣጣሪዎች ወደ ቴህራን እንዲገቡ የሚያስችል ጠንካራ ማዕቀፍ ሊኖረው እንደሚገባም ተገልጿል።
